አንድ ትውልድ ትውልዳዊ ፍሰቱን ጠብቆ  በስኬት መጓዝ ይችል ዘንድ፤  ሃገራት ከቁሳዊ ሥልጣኔ  ባሻገር በመንፈስ የሰለጠነ፤ በሥነ – ምግባር የታነፀና ባለራዕይ ዜጋ ያስፈልጋቸዋል – አቶ አወቀ ገ/መስቀል

ለሚሊነዬም ኮሌጅ አሶሳ ካምፓስ ተማሪዎች የስብዕናና የሞራል እሴቶች ግንባታ በሚል ይዘት  የግንዛቤ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡   ስልጠናውን  የሰጡት የኮሚሽኑ  የፊት ለፊት የሥነ-ምግባር ትምህርትና ስልጠና ባለሙያ አቶ አወቀ ገ/መስቀል  አንድ ትውልድ ትውልዳዊ ፍሰቱን ጠብቆ  በስኬት መጓዝ ይችል ዘንድ፤  ሃገራት ከቁሳዊ ሥልጣኔ  ባሻገር በመንፈስ የሰለጠነ፤ በሥነ – ምግባር የታነፀና ባለራዕይ ዜጋ ያስፈልጋቸዋል ፡፡  ወጣቱም እራሱን በዚሁ ልክ ማዘጋጀት […]

ተጨማሪ ያነቡ

የግብር ከፋዩን ቅሬታ ለመቅረፍ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ወደ ሥራ ያስገባው የካሜራ ቴክኖሎጂ

    የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ ከደረሰኝ ቁጥጥር ጋር በተያያዘ በግብር ከፋዮች ከባለሙያዎች ሥነ-ምግባር ጉድለት ጋር በማያያዝ የሚቀርቡ ቅሬታዎች በተሟላ ደረጃ ለመቅረፍ የሚያስችል ቴክኖሎጂ አልምቶ ወደ ተግባር ማሸጋገሩ ተገለጸ።   የቢሮው ኃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ በደረሰኝ ቁጥጥር ባለሙያዎች ዩኒፍርም ላይ በተገጠመ የካሜራ ቴክኖሎጂ፣ ቢሮው ፍትሃዊ የገቢ አሰባሰብ ለመዘርጋት በቀየሳቸው አሠራሮች፣ በቅሬታ አቀራረብ እና አፈታት እንዲሁም […]

ተጨማሪ ያነቡ

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ተወካይ በ6ኛው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድ (ዶ.ር) ያነሱት ጥያቄ፤

  በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካማሽ ዞን በመብራት ችግር 10 ዓመት፣ በመንገድ ችግር 5 አመት ሁኖናል፣ ዞኑ አምስት ወረዳዎችን ይዞ የተዘጋ ዞን ነው፡፡ በቴሌ ተመሳሳይ ችግር አለ ተማሪዎቻችን መብራት እና ኔትወረክ በሌለበት ሁኔታ ከሌሎች ጋር ተወዳዳሪ መሆን አልቻሉም፡፡ በመፅሐፍ ቅዱስ ታሪክ እግዚአብሔር ሰዶምና ገሞራን ሊያጠፋ ባሰበ ጊዜ ስለ ጥቂት ንፁሃን አብርሐም ምህረት እንዲያደርግ እንደጠየቀው፤ በዚህ ዞንም  […]

ተጨማሪ ያነቡ

የኮሚሽኑን የሙስና መከላከል ስራ ለማጠናከር  የአሰራር ጥናት ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ ነው –  ኮሚሽነር ከማል ሃሰን

  ኮሚሽኑ ከፌዴራል ሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን የአቻ ለአቻ ድጋፋዊ ግምገማ ለማድረግ ከመጣው ቡድን ጋር የመጠቃለያ ውይይት አድርጓል፡፡   ተቋሙ በክልሉ በሚገኙ የመንግስት ተቋማትና የልማት ድርጅቶች ሙስናና ብልሹ አሰራርን ቀድሞ ለመከላከል የአስራር ጥናትን እንደ አንድ ቁልፍ መሳሪያ እየተጠቀመ መሆኑን ኮሚሽነር ከማል ሃሰን በውይይቱ  አውስተዋል፡፡     በዚህ ስራም ለሙስናና ብልሹ አሰራር ተጋላጭ የሆኑ የመንግስት ተቋማት ካላቸው […]

ተጨማሪ ያነቡ

በጣም ደስ ብሎኛል! አሁን ያለምንም ሃሳብ ትምረቴን መማር እችላለሁ – ተማሪ ሰሎሜ ሙሳ (የማንኩሽ 2ኛ ደ/ትቤት ተማሪ)

ኮሚሽኑ የክረምት የበጎ አድራጎት ስራን ምክንያት በማድረግ  ድጋፍ ለሚሹ 100 የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ  ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ በጉባ ወረዳ ማንኩሽ ከተማ አድርጓል፡፡   የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ የተደረገላት ተማሪ ሰሎሜ ሙሳ (የማንኩሽ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪ )  ድጋፉ ያለምንም ሃሳብ ትምህርቷን መማር እንደሚያስችላት ገልፃ፤ በተደረገላት ድጋፍ ደስተኛ መሆኗን ተናግራለች፡፡   በተመሳሳይ ተማሪ ማህሌት አዳነ (የማንኩሽ ሁለተኛ […]

ተጨማሪ ያነቡ

ኮሚሽኑ የ2018 እቅዱን ለመፈፀም የተበጀተለትን ውስን ሃብት በቁጠባና ለታለመለት ዓላማ በማዋል ውጤታማ የሙስና መከላከል ስራዎችን ለመስራት አበክሮ ይሰራል –  ኮሚሽነር ከማል ሃሰን

  ኮሚሽኑ በክልሉ መንግስት ለ2018 እቅድ ማስፈፀሚያ   የተሰጠውን ውስን በጀት በቁጠባና ለታለመለት ዓላማ በማዋል ውጤታማ የሙስና መከላከል ስራዎችን አበክሮ እንደሚሰራ   የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ከማል ሃሰን ገለፁ፡፡   አጠቃላይ የተቋሙን መደበኛና ፕሮግራም በጀት በሚመለከት ከኮሚሽኑ አመራሮችና የሥራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት ያደረጉት ኃላፊው፤  የበጀት አጠቃቀምን  በደንብና መመሪያ በመምራት አፈፃፀምን ማሳደግ እንደሚገባም ነው […]

ተጨማሪ ያነቡ

የኮሚሽኑ አመራሮችና ሰራተኞች በመትከል ማንሰራራት! በሚል መሪ ቃል በያዝነው ክረምት በክልሉ ከ 15 ሚሊዬን በላይ ችግኞችን ለመትከል የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት በሰልጋ 20 ቀበሌ ተገኝተው የችግኝ መትከል መረሃ ግበር አከናውነዋል::

የኮሚሽኑ አመራሮችና ሰራተኞች በመትከል ማንሰራራት! በሚል መሪ ቃል በያዝነው ክረምት በክልሉ ከ 15 ሚሊዬን በላይ ችግኞችን ለመትከል የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት በሰልጋ 20 ቀበሌ ተገኝተው የችግኝ መትከል መረሃ ግበር አከናውነዋል::   እንደ ሃገር በአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ (በዛሬው እለት ብቻ) ከ 700 ሚሊዬን በላይ ችግኞችን ለመትከል መታቀዱና ለተግባራዊነቱ ይህ መረጃ በተጠናቀረበት ሰዓት ኢትዮያውያን እየተረባረቡ መሆኑ ይታወቃል፡፡

ተጨማሪ ያነቡ