20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን “ዲሞክራሲያዊ መግባባት፤ ለህብረ ብሄራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል በአሶሳ ከተማ በክልሉ መስተዳድር አዳራሽ በፓናል ውይይት እየተከበረ ነው፡፡

ወቅታዊ መረጃ

በውይይቱ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ የስራ ኃላፊዎችና የመንግስት ሰራተኞች በመታደም ላይ ሲሆኑ፤ ቀኑን በማስመልከትም የፌዴራሊዝምን አስተምህሮ በሚመለከት ረዳት ፕሮፌሰር አዳሙ ጅባት (የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የፌደራሊዝም መምህር)  የመወያያ ሰነድ በማቅረብ ላይ ናቸው፡፡

 

ከሰነዱ መቅረብ በኋላ ተሳታፊዎች ጥልቅ ውይይት በማድረግ የጋራ ግንዛቤ እንደሚያዝ ይጠበቃል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *