ኮሚሽኑ በካማሺ ዞን በሚገኙ ወረዳዎች የስልጠና እና የድጋፍ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል፡፡

የኮሚሽኑ የሥልጠና፣ የድጋፍናክትትል ቡድን በካማሺ ዞን በዛይ እና ምዥጋ ወረዳዎች በመንቀሳቀስ ለየሴክተር መ/ቤት ማኔጅመንት አካላት፣ ለሥነ-ምግባር መከታተያ ክፍል ባለሙያዎችና የሥነ-ምግባር ፀረሙስና ፎካል ፐርሰኖች በሥራ ሥነ-ምግባር፣ በመንግስት ተቋማት አገልግሎት አሠጣጥና በሙስናና ብልሹ አሰራር ይበልጥ ተጋላጭ በሆኑ የሥራ ዘርፎች ማለትም በፋይናንስ አጠቃቀም፣ በግዥና ንብረት አስተዳደር እንዲሁም በማዕድን ዘርፎች ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማሳደጊያ  ስልጠናዎችን እየሰጠ ይገኛል።   የድጋፍና […]

ተጨማሪ ያነቡ

ሕብረተሰቡ ህግና ሥርዓትን ተከትሎ ፍትህ ማግኘት እንደሚችል ማሳየት ይገባናል – የአሶሳ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ መሀመድ መሀሙድ

ኮሚሽኑ ከአሶሳ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጋር በመተባበር  በፍርድ ቤቶች ስለሚስተዋሉ የሙስናና ብልሹ አሰራር ድርጊቶች፣  በር ስለሚከፍቱ የአሰራር ሂደቶችና መፍትሔዎቻቸውን በሚመለከት ለከፍተኛ ፍርድ ቤቱ  ዳኞችና የአስተዳደር ሰራተኞች ስልጠና ሰጥቷል፡፡   ከሙስናና ብልሹ አሰራር የፀዳ   አገልግሎትን በማድረስ  ሕብረተሰቡ  ህግና ሥርዓትን ተከትሎ ፍትህ ማግኘት እንደሚችል ማሳየት እንደሚገባ የአሶሳ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት አቶ መሀመድ መሀሙድ በዚህ […]

ተጨማሪ ያነቡ

ኮሚሽኑ በካማሽ ዞን ስር ለሚገኙት የሰዳልና ደምቤ ወረዳ አመራሮችና የማኔጅመንት አካላት ስልጠና ሰጠ፡፡

ኮሚሽኑ በካማሽ ዞን ስር ለሚገኙት የሰዳልና ገምቤ ወረዳ የተቋማት አመራሮችና የማኔጅመንት አካላት በፀረ-ሙስና ትግሉ የአመራሩ ሚና በሚል ርዕስ ስልጠና ሰጥቷል፡፡   ስልጠናውን የሰጡት በኮሚሽኑ የፊት ለፊት የሥነ-ምግባር ትምህርትና ስልጠና ባለሙ አቶ አወቀ ገ/መስቀል ከግዥና  ፋይናንስ፣ ከሰራተኛ ቅጥርና ጥቅማጥቅም፣ በማዕድን ዘርፍና  ተጓዳኝ ጉዳዮች ጋር ተያይዞ ስለሚስተዋል  ሙስናና ብልሹ አሰራርና  መወሰድ ስለሚገባው መፍትሔ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡   […]

ተጨማሪ ያነቡ

እንደ ሃገር ጠንካራ ዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ዜጎችን ሁሉን አቀፍ የዲጂታል ክህሎት ማስታጠቅ ለኢትዮጵያ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ስኬት ወሳኝ ነው፡፡

ለውጤታማነቱም በኢትዮጵያ የ5 ሚሊዮን ኮደር መረሐ ግብር ተነድፎ እንደ ሃገር ወደ ስራ መገባቱ የሚታወስ ነው፡፡ ክልላችንም 65 ሽህ አካላትን ማሰልጠን እንዲችል እድል ማግኘቱ የሚታወስ ነው፡፡ ከዚህ በመነሳት ኮሚሽኑ የሥልጠና ፍላጎት ላላቸው የኮሚሽኑ ባለሙያዎችና ሰራተኞች ስልጠናውን በሚመለከት በክልሉ የሳይንስና ቴክኖሎጅ ባለሙያ አቶ ቢኒያም ተፈራ በኩል ገለፃ ተደርጓል፡፡ እንደ ክልልና እንደ ሃገር የምጣኔ ሀብት ዕድገትና ብልፅግናን ለማምጣት […]

ተጨማሪ ያነቡ

ውጤታማ የሙስና መከላከል ስራዎችን ለመስራት ቴክኖሎጅን በግብዓትነት መጠቀም እንደሚያስፈልግ ተገለፀ፡፡

ኮሚሽኑ የሐብት ማስመዝገብና ማሳወቅ መረጃዎች ሚስጥራዊነቱ የተጠበቀ፣  ወጭና ጊዜን ሊቆጥብ በሚችል መልኩ መያዝ የሚያስችለውን የመረጃ አያያዝ ሥርዓት ከክልሉ ሳይስና ቴክኖሎጅ ኤጀንሲ ጋር በመተባበር ሲያስለማ መቆየቱን የገለፁት በኮሚሽኑ የሐብት ማስመዝገብና ማሳወቅ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ኤሊያስ ወዲሻ ናቸው፡፡   ይህም  ውጤታማ የሙስና መከላከል ስራዎችን በመስራት   ረገድ የሐብት ምዝገባ መረጃዎችን ደህንነት ለመጠበቅ እና  ቀልጣፋ አሰራር ለመዘርጋት እንደሚያስችል  ዳይሬክሩ […]

ተጨማሪ ያነቡ

ት/ቤቶች በመልካም ሥነ-ምግባር የታነፀ ትውልድ ለመገንባት በሚደረገው ጥረት የሚጠበቅባቸውን ሚና ሊወጡ እንደሚገባ ተገለፀ፡፡

(ቶንጎ፣ ታህሳስ 11/2017 ዓ.ም) ት/ቤቶች በሥነ-ምግባ የታነፀ እና በዕውቀት የተካነ ማህበረሰብ ለመገንባት በሚደረገው ጥረት የበኩላቸውን ሚና እየተወጡ እንደሆነ የማኦ ኮሞ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ም/ርዕሰ መምህር እስራኤል መልካ ገለፁ፡፡ ለዚህም በት/ቤቱ በስራ ላይ የሚገኘውን የግብረ-ገብና የፀረ-ሙስና ክብብ የተማሪዎችን ባህሪ ለማስተካከልና እና ውጤታውን ለማሻሻል እየተጠቀሙበት እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ በተመሳሳይ በቶንጐ ከተማ የሚገኘው የአባ ሃሩን አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ም/ርዕሰ […]

ተጨማሪ ያነቡ

ስራ ስነ-ምግባር መልካም አስተዳደርን ለማስፈንና ዘርፈ ብዙ ዉጤታማነትን ለማሳደግ የጎላ ሚና አለው – አቶ ገዛኸኝ የኔው

የስራ ስነ-ምግባር መልካም አስተዳደርን ለማስፈንና ዘርፈ ብዙ ዉጤታማነትን ለማሳደግ የጎላ ሚና አለው – አቶ ገዛኸኝ የኔው (ቶንጎ ፣ ታህሳስ 10/2017 ዓ.ም) ኮሚሽኑ በማኦ ኮሞ ልዩ ወረዳ ለሚሰሩ አመራሮችና የመንግስት ሰራተኞች የሥራ ሥነ-ምግባርን በሚመለከት የግንዛቤ ሥልጠና ሰጠ፡፡ ስልጠናውን የሰጡት በኮሚሽኑ የትምህርትና ስልጠና ቡድን መሪ አቶ ገዛኸኝ የኔው የሥራ ስነ-ምግባር መልካም አስተዳደርን ለማስፈንና ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ውጤታማነትን […]

ተጨማሪ ያነቡ

ሙስናና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል ከክልሉ የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ጋር በቅርበት እንደሚሰራ የማኦ ኮሞ ልዩ ወረዳ አስታወቀ፡፡

ሙስናና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል በሚደረግ ዘርፈ ብዙ መተጋገል ከኮሚሽኑ ጋር በቅርበት መስራት እንደሚፈልጉ የማኦ ኮሞ ልዩ ወረዳ ም/አስተዳዳሪ አቶ መሐመድ ሐብቴ ገልፀዋል፡፡   ም/አስተዳዳሪው አክለውም ሙስናና ብልሹ አሰራር ለመከላከል ልዩ ወረዳው  በሚያደረገው ጥረት ኮሚሽኑ ቀጣይነት ያለው  የሙስና መከላከል ስራ   (የሥልጠና፣ የሐብት ምዝገባ፣   የድጋፍና የክትትል ስራዎችን) በመስራት  እንዲያግዛቸው ጠይቀዋል፡፡   ኮሚሽኑ በማኦ ኮሞ ልዩ ወረዳ የሙስና […]

ተጨማሪ ያነቡ

ኮሚሽነር መንግስቱ ላሎ በሃገራችን ለ20ኛ (በአለም ለ21ኛ) ጊዜ በተከበረው የአለም የፀረ-ሙስና ቀን ክልል አቀፍ የማጠቃለያ መድረክ ያስተላለፉት መልዕክት፤

ተጨማሪ ያነቡ