የ2015 የመጀመሪያው ሩብ አመት የኮሚሽኑ ሪፖርት ለማኔጅመንት አካላት እና ለሚመለከታቸው የሥራ ክፍሎች ቀርቦ ተገመገመ፡፡ በሪፖርቱ በሐብት ማጣራት፣ በስልጠና፣ በክትትልና ድጋፍ እንዲሁም በአሰራር ጥናት ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸው ተመላክቷል፡፡ በቀጣይም ሙስናና ብልሹ አሰራርን በመከላከል ውጤታማ ስራ ለመስራት የሚያስችል የትኩረት አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡

ተጨማሪ ያነቡ

የኮሚሽኑ ባለሙያዎች ሙያዊ ድጋፍና እገዛ አደረጉ፤

የኮሚሽኑ ባለሙያዎች በመንጌ ወረዳ በመገኘት ለሙስናና ብልሹ አሰራር መተጋገል እንደሚያግዝ የታመነበት ሙያዊ ድጋፍ ለወረዳው አመራሮችና የሥነ-ምግባር መከታተያ ክፍሎች አደረጉ፡፡ ከኮሚሽኑ የሃብት ምዝገባ እና የሙስና መከላከል ዳይሬክተሮች የተወጣጡ የኮሚሽኑ ባለሙዎች በሃብት ማስመዝገብና ማሳወቅ እንዲሁም በሙስናና መከላከል እስትራቴጅዎች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ድጋፍ አድርገዋል፡፡ የመንጌ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ኢብራሂም መንሱር ድጋፉን አስመልክቶ በሰጡት አስተያየት እገዛው እጅግ ጠቃሚ መሆኑን […]

ተጨማሪ ያነቡ

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን እና የክልሉ ወሳኝ ኩነት ኤጀንሲ በትብበር በመስራት ተልዕኳቸውን ለመፈፀም የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረሙ፡፡ ***************

የትብብር ሰነዱ ሁለቱ ተቋማት በጋራ በመስራት እንደ ክልልና እንደ ሃገር የተሰጣቸውን ኃላፊነት በአግባቡ ለመወጣት የሚያግዝ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ በሰነዱ በስነ-ምግባር ግንባታ፣ ሙስና መከላከልና መልካም አስተዳደር ስልጠና፣ በኮምዩኒኬሽንና የህዝብ ግንኙነት ስራዎች፣ የአይሲቲ ውጤቶች አጠቃቀም፣ አሰራርና አደረጃጀቶች፣ ወቅታዊ እና አስፈላጊ የሆኑ ሙያዊ የምክር አገልግሎቶች እንዲሁም ሌሎች በሁለቱ ተቋማት ፍላጎቶች መሰረት ባደረጉ ጉዳዮች በትብብር እንደሚሰራ ሰነዱን ያቀረቡት አቶ ባዛብህ […]

ተጨማሪ ያነቡ

ኮሚሽኑ ለመከታተያ ክፍሎች እያደረገ ያለው ዘርፈ ብዙ እገዛ የመከታተያ ክፍሎች ስራቸውን ተረጋግተው እንዲሰሩና በፀረ-ሙስና ትግሉ ውጤት እንዲያስመዘግቡ የሚያግዝ መሆኑ ተገለፀ፡፡ *******************

በሸርቆሌ ወረዳ የኢኮኖሚ ዘርፍ የሥነ-ምግባር መከታተያ ክፍል ባለሙያ አቶ አልታሰብ ቢሌ በአዲሱ የበጀት አመት አመርቂ የሙስና መከላከል ስራዎችን ለመስራት የሚያስችላቸውን የዕቅድ ማናበብና ለስራቸው መሳሪያ የሚሆናቸውን ስልጠናዎች መውሰዳቸውን ከስራ ክፍላችን ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልፀዋል፡፡ በተያዘው የበጀት አመትም ከኮሚሽኑ ዕቅድ ጋር በሚጣጣም መልኩ አቅደው ወደ ስራ መግባታቸውን አቶ አልታሰብ ቢሌ ተናግረዋል፡፡ ከስልጠና ባለፈም ኮሚሽኑ ለስራችን ስኬታማነት ምቹ […]

ተጨማሪ ያነቡ

ለፀረ-ሙስና ትግሉ የፍትህ አካላት መጠናከርና የማህበረሰቡ ቁርጠኝነት ሚናው የላቀ ነው፡፡ *******************

አቶ ሲሳይ ጌታነህ (በባምባሲ ወረዳ የአስተዳደር ዘርፍ የሥነ-ምግባር መከታተያ ክፍል ባለሙያ) ሙስናና ብልሹ አሰራር ዛሬ ላይ ድርሻው ይለያይ እንጅ በየትኛውም ዘርፍ ላይ እንደሚስተዋል በስራቸው መታዘባቸውን ይገልፃሉ፡፡ ነገር ግን በትምህርቱ ዘርፍና እና በሰራተኛ ቅጥር፣ ዝውውር ተያያዥ ጉዳዮች የሚፈፀመው ሌብነት አይን ያወጣና የሚያደርሰው ጉዳትም እንደሳቸው ገለፃ የከፋ ነው፡፡ የትምህርቱ ዘርፍ የማህበረሰብን አስተሳሰብ በላቀ እውቀት በመገንባት የተሻለ ሃገርና […]

ተጨማሪ ያነቡ

’በቅንጅትና በትብብር ከሰራን በፀረ-ሙስና ትግሉ የሚፈለገው ውጤት ላይ እንደርሳለን፡፡’’ መንግስቱ ላሎ (ኮሚሽነር)

(ባምባሲ፤21/2015 ዓ.ም) በቅንጅትና በትብብር ከሰራን በፀረ-ሙስና ትግሉ የሚፈለገው ውጤት ላይ እንደርሳለን ሲሉ ኮሚሽነር መንግስቱ ላሎ ተናገሩ፡፡ ይህን ያሉት በባምባሲ ከተማ ከኮሚሽኑ ጋር በጥምረት ከሚሰሩ (የህዝብ ክንፍ) ባለድርሻ አከላት ጋር የኮሚሽኑን ያለፈ አመት አፈፃፀም እና ቀጣይ እቅድ በሚመለከት ውይይት በተደረገበት መድረክ ነው፡፡ በዚሁ መድረክ የተገኙት ክብርት ወ/ሮ አለምነሽ ይባስ (የክልሉ ምክር ቤት ም/አፈጉባኤ እና የሴቶች ፌዴሬሽን […]

ተጨማሪ ያነቡ