በአሶሳ ዞን ስር የሚገኙ ወረዳዎች የሐይማኖት ተቋማት የፀረ-ሙስና ንቅናቃ ጥምረት አፈጻጸም ግምገማ ተካሄደ፡፡ ***********************

ወቅታዊ መረጃ

በአፈጻጸም ግምገማው ላይ የተገኙ አባቶች የሐይማኖት ተቋማት ከሙስናና ብልሹ አሰራር በመራቅ ለተከታዮቻቸው አርዓያ መሆን እንዳለባቸው  ተናግረዋል ፡፡

በውይይቱ ላይ ተገኝተው መድረኩን የመሩት ም/ኮሚሽነር ዑሳም ሃሊፋ ባስተላለፉት መልዕክት «እዚህ የተገኛችሁ የሃይማኖት አባቶች ዘርፎ መክበርን፣ ሰርቆ አለማፈርን የሚያበረታታውን አስተሳሰብ እያወገዛችሁ እና ለተከታዮቻችሁ መልካም ሥነ-ምግባርን እያስተማራችሁ፤እናንተም መልካም ተምሳሌት በመሆን ለትውልዱ መልካም ሥነ-ምግባርን ማውረስ ይጠበቅባችኋል » ብለዋል ፡፡

በኮሚሽኑ የሙስናና ብልሹ አሰራሮች መከላከል ዳ/ዳይሬክተር አቶ ገመዳ ቡሊ በውይይቱ ማጠቃለያ ላይ እንደተናገሩት «የነገ ሃገር ተረካቢ ትውልድ እጣ ፈንታ የሚወሰነ ዛሬ በሚሰጡ  የመልካም ሥነ-ምግባር አስተምህሮቶች በመሆኑ የሃይማኖት አባቶች በየተቋሞቻቸው ይህንን ሐላፊነት በመውሰድ ወጣቶችን በመልካም ሥነ-ምግባር የማነጽ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ መወጣት አለባችሁ » ብለዋል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *