የዘንድሮው የሰንደቅ ዓላማ ቀን ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን አስመርቀን በአብሮነት በደመቅንበት ማግሥት የሚከበር መሆኑ ልዩ ያደርገዋል፡፡ የተከበሩ አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ አስካለች አልቦሮ

ወቅታዊ መረጃ


‎**************
‎(አሶሳ፣ ጥቅምት 03/2018 ዓ.ም) የዘንድሮው የሰንደቅ ዓላማ ቀን ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን አስመርቀን በአብሮነት በደመቅንበት ማግሥት የሚከበር መሆኑ ልዩ እንደሚያደርገው የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ አስካለች አልቦሮ አስታወቁ።

አክለውም የላብ፣ የውሃና የደም ጠብታ ውጤት የሆነውን ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በማጠናቀቅ የአባቶቻችንን ታሪክ አድምቀን የጻፍንበት ጊዜ ላይ እንገኛለን ብለዋል፡፡

‎ሰንደቅ ዓላማችን የሃገራችን የሉዓላዊነት እና የነጻነት ምልክታችን ነው ያሉት ወ/ሮ አስካለች፣ ብሔራዊ አርማ ለሆነው ሰንደቅ ዓላማ የሚገባውን ክብር መስጠት ተገቢም አስፈላጊም መሆኑን አስታውሰዋል፡፡

‎በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል 18ኛው ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን “ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጲያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ” በሚል መሪ ቃል በክልሉ መስተዳድር ግቢ ተከብሯል፡፡

‎የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሃሰን እና የክልሉ ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ አስካለች አልቦሮ እለቱን ምክንያት በማድረግ ሰንደቅ ዓላማ የማውጣት ሥነ-ሥርዓት ፈፅመዋል።

በሥነ-ሥርዓቱ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ የሥራ ኃላፊዎችና የፀጥታ አካላት የተገኙ ሲሆን፤ ለሁነቱ የክልሉ የፖሊስ ማርች ባንድ ከፍተኛ ድምቀት ሰጥተውታል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *