
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የማዕድን ቦርድ ትላንት ባካሄደው ስብሰባ በማዕድን ሀብት ላይ የሚስተዋለውን ሕገ-ወጥ አሠራር ለመከላከል የጀመራቸውን የቁጥጥር ሥራዎች የበለጠ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል፡፡
በክልሉ ያለውን የማዕድን ሀብት የአካባቢ ተጽእኖን በቀነሰ እና ዘላቂ ተጠቃሚነትን ባረጋገጠ መልኩ መጠቀም እንደሚገባም ቦርዱ አፅንኦት ሰጥቷል፡፡
በሌላ በኩል በተለያዩ የማዕድን ዘርፎች ወደ ሥራ ለመግባት ፈቃድ ተሰጥቷቸው ወደ ልማት ያልገቡ ባለሃብቶች ፈቃድ እንዲሰረዝም ቦርዱ ወስኗል።
በተጨማሪም በክልሉ በማዕድን ሀብቶች ልማት ለመሠማራት የቀረቡ አዳዲስ ጥያቄዎችን ተገቢነት መርምሮ ውሳኔ ማሳለፉን የዘገበው የክልል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ነው፡፡
