በ UIIDP የገንዘብ ድጋፍ በአሶሳ ከተማ የተሰሩ የመሰረተ-ልማቶች አፈፃጸም ግምገማ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ በ UIIDP የገንዘብ ድጋፍ በአሶሳ ከተማ የተሰሩና እየተሰሩ ያሉ የመሰረተ-ልማቶች ያሉበት ደረጃ ከፌደራል የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በተወጣጡ ሰባት አባላትን ባካተተ የጥናት ቡድን የማረጋገጥ ሥራ በመስራት ላይ ይገኛል፡፡ የጥናት ቡድኑ ትኩረት ካደረገባቸው ጉዳዮች መካከል፤ በፕሮጀክቶች አፈፃፀም ወቅት ፤ሙስናን መከላከል የሚያስችሉ የአሰራር ስርዓት መኖር፤ […]

ተጨማሪ ያነቡ

ዜና መፅሔታችን እንኋት፤ ጊዜዋን ጠብቃ ለንባብ በቅታለች፡፡ በውስጧ በአመቱ ኮሚሽኑ የተቀናጃቸውን አንኳር ስኬቶች በተመጠኑ ቃላት እምቅ ክዋኔዎችን ታስቃኛለች፡፡ አንብባችሁ ሃሳብ አስተያየታችሁን ብትሰጡን ታጠነክሩናላችሁ፡፡ መልካም ንባብ!

ተጨማሪ ያነቡ

የኮሚሽኑ የ2015 ዓ/ም አመታዊ አፈፃፀም

ኮሚሽኑ ከተሰጠው ተልዕኮ አንፃር   በበጀት አመቱ በእቅድ ይዞ ሲሰራባቸው ከነበሩ ተግባራት 84.64 ከመቶ የሚሆነውን በስኬት ማጠናቀቁን ሪፖርቱን በአስተዳደር አባላት በገመገመበት ወቅት አስታውቋል፡፡ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በበጀት አመቱ በክልሉ የሙስና መከላከል ስራዎችን ውጤታማነት ለማሳደግ አመርቂ ተግባራትን ሲሰራ መቆየቱን ኮሚሽነር መንግስቱ ላሎ ገልፀዋል፡፡ የሥነ-ምግባር ትምህርትና ስልጠና፣ አስቸኳይ የሙስና መከላከል፣ የአሰራር ጥናት ማካሄድና ማማከር፣ […]

ተጨማሪ ያነቡ

ከ128, ዐዐዐ በላይ ለሚሆኑ አካላት ስራቸውን በተሻለ ሥነ-ምግባር መስራት የሚያስችል ስልጠና መስጠት መቻሉን ኮሚሽኑ አስታወቀ፡፡ ****************

ከ128, ዐዐዐ በላይ ለሚሆኑ አካላት ስራቸውን በተሻለ ሥነ-ምግባር መስራት የሚያስችል ስልጠና መስጠት መቻሉን ኮሚሽኑ አስታወቀ፡፡ **************** (አሶሳ፣ ግንቦት 23/2ዐ15፤ ቤጉ-ፀረ-ሙስና) የቤኒቫንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን 128,076 ለሚሆኑ የህ/ሰብ ክፍሎች የሥነ-ምግባር ስልጠናዎች መስጠት መቻሉን ኮሚሽነር መንግስቱ ላሎ ገልፀዋል፡፡   በስልጠናው ሙያዊ ሥነ-ምግባር፣ የሞራል እሴቶች እና ሥነ-ምግባራዊ አመራር ከተሰጡት የሥልጠና ርዕሶች ጥቂቶቹ መሆናቸው በያዝነው የበጀት […]

ተጨማሪ ያነቡ

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በዘጠኝ ወር አፈፃፀሙ ከ36 ሚሊየን ብር በላይ ከምዝበራ ማዳኑን አስታወቀ፡፡

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በዘጠኝ ወር አፈፃፀሙ ከ36 ሚሊየን ብር በላይ ከምዝበራ ማዳኑን አስታወቀ፡፡ *************** (አሶሳ፤ ግንቦት 21/2015፤ ቤጉ ፀረ-ሙስና) ኮሚሽኑ ከ36, 398,358.93 ከምዝበራ ማዳኑን የ9 ወር አፈፃፀሙን በገመገመበት ወቅት ገልጧል፡፡ ለስራው ውጤታማነትም ከድርጅቶችና ከግለሰቦች 68 ጥቆማዎች መቀበሉ ተመላክቷል፡፡ ተቋሙ የተሰጠው ዋነኛው ተልኮ አስቸኳይ የሙስና መከላከል (ሙስና ከመከሰቱ በፊት የሚመዘበር የመንግስትና የህዝብን […]

ተጨማሪ ያነቡ

ፌደራል ፀረ-ሙስና እና ክልሎች ውይይት

በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የወንጀል መከላከል እና የዕፅ ቁጥጥር ቢሮ (UNODC) እና የፌዴራል የሥነ-ምግባና ፀረ-ሙስና ኮሚሽ ትብብር “የንግድ ስራ ሀቀኝነትን ለማሳደግ የግሉን ዘርፍ አቅም ማጎልበት” በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ውይይት በአዲስ አበባ በመካሄድ ላይ ነው፡፡ በመድረኩ የክልል የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ተወካዮች፣ የመንግስት ከፍተኛ ኃላፊዎችና የአለም አቀፍ ተቋማት ኃላፊዎች፣ የግሉ ዘርፍ ተወካዮችና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ተገኝተዋል። See insights […]

ተጨማሪ ያነቡ

በሙስና ምክኒያት 2.2 ቢሊዮን ብር የህዝብና የሀገር ሀብት ለብክነት መዳረጉን ሀገራዊ የፀረ ሙስና ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ ተመስገን ጥሩነህ አስታወቁ:: *****************************

የብሄራዊ አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት እስካሁን በተከናወኑ የሙስና ተግባር 759 የሙስና ወንጀሎች ከህብረተሰቡ ጥቆማ የቀረበ ሲሆን፤ ከተጠቆሙት መካከል 175 የሙስና ወንጀሎች በመለየት ምርመራ እየተደረገበት እንደሆ ገልፀዋል። ከዚህ ውስጥ በ81 ላይ ክስ በመመስረት ተጠያቂነት እያደረጉ መሆኑን ጠቁመው። 2.2 ቢሊዮን ብር የህዝብና የመንግስት ሀብት ለብክነት መዳረጉን የኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ ተመስገን ጥሩነህ ገልፀዋል። 640 የሚሆኑ ግለሰቦች ክስ በመመስረት ግለሰቦች […]

ተጨማሪ ያነቡ

በአሶሳ ዞን ስር የሚገኙ ወረዳዎች የሐይማኖት ተቋማት የፀረ-ሙስና ንቅናቃ ጥምረት አፈጻጸም ግምገማ ተካሄደ፡፡ ***********************

በአፈጻጸም ግምገማው ላይ የተገኙ አባቶች የሐይማኖት ተቋማት ከሙስናና ብልሹ አሰራር በመራቅ ለተከታዮቻቸው አርዓያ መሆን እንዳለባቸው  ተናግረዋል ፡፡ በውይይቱ ላይ ተገኝተው መድረኩን የመሩት ም/ኮሚሽነር ዑሳም ሃሊፋ ባስተላለፉት መልዕክት «እዚህ የተገኛችሁ የሃይማኖት አባቶች ዘርፎ መክበርን፣ ሰርቆ አለማፈርን የሚያበረታታውን አስተሳሰብ እያወገዛችሁ እና ለተከታዮቻችሁ መልካም ሥነ-ምግባርን እያስተማራችሁ፤እናንተም መልካም ተምሳሌት በመሆን ለትውልዱ መልካም ሥነ-ምግባርን ማውረስ ይጠበቅባችኋል » ብለዋል ፡፡ በኮሚሽኑ […]

ተጨማሪ ያነቡ