የኢፌዴሪ የሀገር መከላከያ ሠራዊት የምዕራብ ዕዝ 404ኛ ህዳሴ ኮር 3ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በኪነ-ጥበብ ስራዎችና በተለያዩ ዝግጅቶች በአሶሳ ከተማ በድምቀት እየተከበረ ነው፡፡
በበዓሉ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት ም/ርዕሰ መስተዳድር የተከበሩ አቶ ጌታሁን አብዲሳን ጨምሮ የዕዙ ከፍተኛ አመራሮችና የክልሉ ባለስልጣናት፣ የክልሉ የፀጥታ አካላት እንዲሁም የሀገር ሽማግሌዎች በመታደም ላይ ናቸው፡፡


