የሐይማኖት አባቶች የሙስናን አስከፊነት ለምዕመናን በማስተማር ሀገራዊ ግዴታቸውን እንዲወጡ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ጥሪ አቀረበ።
ኮሚሽኑ ለሐይማኖት ተቋማት የፀረ-ሙስና ንቅናቄ ጥምረት “በፀረ ሙስና ትግል የሃይማኖት አባቶች ሚና” በሚል ርዕሰ ጉዳይ ስልጠና ተሰጥቷል።
በስልጠና መድረኩ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ከማል ሀሰን እንዳሉት የሐይማኖት አባቶች በየቤተ-እምነታቸው ትውልዱን በስነ-ምግባር ከማነፅ ባለፈ የሙስናን አስከፊነት ተረድተው ምዕመናኖቻቸውን በማስተማር ሀገራዊ ግዴታቸውን እንዲውጡ ጥሪ አቅርበዋል።
ሙስና በሀገር ላይ የሚያስከትለው ሁለንተናዊ ተፅዕኖ እጅግ የከፋ ነው ያሉት ኮሚሽነሩ ዜጎች በየተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶችን ከሙስና በፀዳ መልኩ ማግኜት ይገባቸዋል ብለዋል፡፡
ሙስናን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በሚደረገው ጥረት ሁሉም ባለድረሻ አካላት የበኩሉን ድጋፍ እንዲያደርምም ኮሚሽነሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የኮሚሽኑ የሙስና ወንጀሎችና ብልሹ አሰራር መከላከል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጊሳ ዚፋህ በበኩላቸው የሐይማኖት አባቶች የሙስናን አፀያፊነትና የሚያስከትለውን ውስበስብ ተፅዕኖ ተረድተው እንዲሰሩ ጠይቀዋል፡፡
ኮሚሽኑ በስነ-ምግባር ጉድለት ምክንያት ሙስና የሚፈፀሙ አካላትን ቀድሞ የመከላከልና የመቆጣጠር ተግባር እያከናወነ ይገኛልም ብለዋል፡፡
በፀረ-ሙስና ትግል የሐይማኖት አባቶች ሚና” በሚለው ርዕሰ ጉዳይ በተዘጋጀው ስልጠና የተሳተፉ የሐይማኖት አባቶች እንዳሉት ሙስና መስጠትም ሆነ መቀበል በሐይማኖታዊ አስተምህሮ ውስጥ ኃጢያት መሆኑን ጠቅሰዋል።
# BGM

