ኮሚሽኑ ድጋፍ ለሚሹ 13 ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ፡፡

ወቅታዊ መረጃ

የኮሚሽኑ አመራሮችና ሰራተኞች 13350 ብር የሚገመት የትምህርት ቁሳቁስ፤ ድጋፍ ለሚሹ 13 ተማሪዎች ለግሰዋል፡፡

 

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ም/ኮሚሽነር  ነጅመዲን አልመሃዲ ድጋፉን ባበረከቱበት  ወቅት እንዳሉት ተማሪዎች በስነ-ምግባራቸው የተመሰገኑ፣  በትምህርታቸው ጠንካራ  መሆን እንደሚገባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡  ይህን ሰናይ ተግባርም ተቋሙ አጠናክሮ  እንደሚቀጥል ጠቁመዋል፡፡

 

የተቋሙ አመራሮችና ሰራተኞች 13  ተማሪዎችን በየአመቱ በቋሚነት እንደሚደግፉ የሚታወቅ ነው፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *