
የተማሪዎችን ስብዕና መገንባት አላማ ያደረገ ሥልጠና ለብራይት ሜዲካል ኮሌጅ አሶሳ ካምፓስ ተማሪዎች ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
ወጣቶች እራሳቸውን በሥነ-ምግባር በመግራት እና እራሳቸውን በመቆጣጠር ሕይወታቸውን በምክንያታዊነት መምራት እንደሚጠበቅባቸው የኮሚሽኑ የፊት ለፊት የሥነ-ምግባር ትምህርትና ስልጠና ባለሙያ አቶ አወቀ ገ/መስቀል ትምህርቱን በሰጡበት ወቅት ተናግረዋል፡፡
የህክምና ሙያ በጥብቅ ሥነ-ምግባር መመራት አለበት ያሉት አቶ አወቀ ተማሪዎች በቀጣይ ወደ ስራው አለም በሚሰማሩበት ወቅትም ማህበረሰብን በመልካም ስነ-ምግባር ማገልገል እንደሚጠበቅባቸው ጠቁመዋል፡፡
አያይዘውም ወጣቱ ከማህበረሰብ ባህልና ወግ ካፈነገጡ ልማዶች እራሳቸውን በመጠበቅ ለዓላማቸው እንዲተጉ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
በመድረኩ ከ300 በላይ ተማሪዎች ሥልጠናውን ወስደዋል፡፡
