ኮሚሽኑ የ2018 እቅዱን ለመፈፀም የተበጀተለትን ውስን ሃብት በቁጠባና ለታለመለት ዓላማ በማዋል ውጤታማ የሙስና መከላከል ስራዎችን ለመስራት አበክሮ ይሰራል –  ኮሚሽነር ከማል ሃሰን

- ወቅታዊ መረጃ

 

ኮሚሽኑ በክልሉ መንግስት ለ2018 እቅድ ማስፈፀሚያ   የተሰጠውን ውስን በጀት በቁጠባና ለታለመለት ዓላማ በማዋል ውጤታማ የሙስና መከላከል ስራዎችን አበክሮ እንደሚሰራ   የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ከማል ሃሰን ገለፁ፡፡

 

አጠቃላይ የተቋሙን መደበኛና ፕሮግራም በጀት በሚመለከት ከኮሚሽኑ አመራሮችና የሥራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት ያደረጉት ኃላፊው፤  የበጀት አጠቃቀምን  በደንብና መመሪያ በመምራት አፈፃፀምን ማሳደግ እንደሚገባም ነው ያስገነዘቡት ፡፡

 

የተቋሙን የማስፈፀሚ በጀት ያቀረቡት የኮሚሽኑ የዕቅድ ዝግጅት ባለሙያ አቶ ቶሎሳ ጅግልዱ ናቸው፡፡

 

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *