
ስልጠናው የተማሪዎችን ስብዕና በመገንባት፣ በተለይም ተማሪዎች ከኮሌጅ ትምህርት በኋላ በሚሰማሩበት የስራ መስክ፤ ለማህበረሰቡ የተሻለ አገልግሎት ለማድረስ እንደሚያስችል ስልጠናውን የሰጡት የኮሚሽኑ የፊት ለፊት የሥነ-ምግባር ትምህርትና ስልጠና ባለሙያ አቶ ንጋቱ ጌታሁን ገልፀዋል፡፡
የመልካም ስብዕና ባለቤት መሆንም የራስን ዓለማና ራእይ ለማሳካትና በህይወት ስኬትን ለመጎናፀፍ እንደሚያግዝ፣ ከዚህ ሲያልፍም ለማህበረሰብና ለሃገር ሁለንተናዊ እድገት ሚናው የላቀ መሆኑን አሰልጣኙ አስገንዝበዋል፡፡
