
ለገመሃሮ ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች የስብዕናና የሞራል እሴቶች ግንባታ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
ስልጠናውን የሰጡት የኮሚሽኑ የፊት ለፊት የሥነ-ምግባር ትምህርትና ሥልጠና ባለሙያ አቶ ንጋቱ ጌታሁን ተማሪዎች ከመደበኛው ትምህርት ጎን ለጎን ከፍ ያለ ስብእናና ሞራልን ሊገነቡ እንደሚገባ ገልፀው፤ መልካም ሥነ-ምግባር ዓለማቸውን ለማሳካትም አንዱና ዋነኛው መሳሪያ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
ባለሙያው አክለውም ምንም ያህል ዕውቀትና ችሎታ ብንጎናፀፍ እንኳን በስነ-ምግባር ካልተመራ ትርጉም የለውም ነው ያሉት፡፡
በዚህ ስልጠና ከ300 በላይ ተማሪዎች ስልጠናውን ወስደዋል፡፡
