የሕክምና ባለሙያዎች በመልካም ሥነ-ምግባር ማህበረሰብን እዲያገለግሉ ጥሪ ቀረበ፡፡

የሕክምና ባለሙያዎች በመልካም ሥነ-ምግባር ማህበረሰብን እዲያገለግሉ ጥሪ ቀረበ፡፡ ም/ኮሚሽነር ኦሳማ ከሊፋ የህክምና ባለሙያዎች ለሙስናና ብልሹ አሰራር የሚያጋልጡ ሂደቶችን በማረም በመልካም ሥነ-ምግባር ማህበረሰብን ማገልገል፤ እንደሚገባ ገለፁ፡፡ ከሰሞኑ ተቋሙ በተለያዩ የጤና ተቋማት ባካሄደው የዳሰሳ ጥናት የአገልግሎት አሰጣጥና የአሰራር ክፍተቶች መኖራቸውን ለይቷል፡፡ ይህንንም መነሻ በማድረግ ለመንጌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል፣ መንጌ ጤና ጣቢያና የአቡጀንዱ ጤና ጣቢያ የህክምና ባለሙዎች፣ አመራሮችና […]

ተጨማሪ ያነቡ

ኮሚሽኑ አቅም ለሌላቸው ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች የገንዘብ እና የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ፡፡

ኮሚሽኑ አቅም ለሌላቸው ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች የገንዘብ እና የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ፡፡ ተማሪዎች የኮሚሽኑ ሰራተኞች ልጆች ናቸው፤ ያሉት የኮሚሽኑ ተወካይ አቶ አበራ ሐምቢሳ ተማሪዎች በሥነ-ምግባርና በትምህርታቸው አርዓያ መሆን እነደሚገባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ የተቋሙ አመራሮችና ሰራተኞች ከደሞዛቸው በማዋጣት ከ11 በላይ ተማሪዎችን በቋሚነት እንደሚደግፉ ይታወቃል፡፡

ተጨማሪ ያነቡ

“ሕብረ ብሄራዊ ወንድማማችነትና እህትማማችነት ለሁለንተናዊ ብልፅግና!” በሚል መሪ ሃሳብ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ከተማ ህዝባዊ ውይይት እየተካሄደ ነው፡፡

ሕዝባዊ ውይይቱን የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ እና የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ/ር) የመሩት ሲሆን በመድረኩ ህብረ ብሄራዊ አንድነትን ፣ ሰላምና ፍቅርን እንዲሁም ልማትን የሚያጠናክሩ ሀሳቦች ተነስተውበታል፡፡ በውይይቱ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከፍተኛ አመራሮች፣ የሥራ ኃላፊዎች እና የማህበረሰብ ተወካዮች ተገኝተዋል ፡፡

ተጨማሪ ያነቡ

በ UIIDP የገንዘብ ድጋፍ በአሶሳ ከተማ የተሰሩ የመሰረተ-ልማቶች አፈፃጸም ግምገማ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡

በ UIIDP የገንዘብ ድጋፍ በአሶሳ ከተማ የተሰሩ የመሰረተ-ልማቶች አፈፃጸም ግምገማ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ በ UIIDP የገንዘብ ድጋፍ በአሶሳ ከተማ የተሰሩና እየተሰሩ ያሉ የመሰረተ-ልማቶች ያሉበት ደረጃ ከፌደራል የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በተወጣጡ ሰባት አባላትን ባካተተ የጥናት ቡድን የማረጋገጥ ሥራ በመስራት ላይ ይገኛል፡፡ የጥናት ቡድኑ ትኩረት ካደረገባቸው ጉዳዮች መካከል፤ በፕሮጀክቶች አፈፃፀም ወቅት ፤ሙስናን መከላከል የሚያስችሉ የአሰራር ስርዓት መኖር፤ […]

ተጨማሪ ያነቡ