ሙያዊ ሥነ-ምግባርን በመላበስ  ህብረተሰቡ የሚፈልገውን አገልግሎት  መስጠት ይገባል –  አቶ አለም ደበሎ

  ሙያዊ ሥነ-ምግባርን በመላበስ፤ ህብረተሰቡ የሚፈልገውን  አገልግሎት በማድረስ ይገባል፡፡ ይህን ስናደርግ ሙስናና ብልሹ አሰራር  በተቋምና በሃገር ላይ ሊያደርስ የሚችለውን ኪሳራ ቀድመን  መከላከል እንችላለን፡፡   በዚህ ረገድ የተቋሙ ሰራተኞች ሙያዊና የዜግነት ግዴታቸውን አበክረው  እንዲወጡ  የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት  ጤና ቢሮ ም/ ቢሮ ኃላፊ አቶ አለም ደበሎ ተናግረዋል፡፡   ም/ቢሮ ኃላፊው ይህን ያሉት የክልሉ ጤና ቢሮና ተጠሪ […]

ተጨማሪ ያነቡ

በመንጌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል 22ኛው የአለም የፀረ-ሙስና ቀን በዓል ትውልድን በሥነ-ምግባር ተቋምን በአሰራር! በሚል መሪ ቃል ተከብሯል፡፡

    እለቱን ምክንያት በማድረግም የመወያያ ሰነድ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተደርጓል፡፡ በውይይቱ የሆስፒታሉ አመራሮችና ሰራተኞች  ደንብና  መመሪያን ተከትለው መስራት  እንደሚገባቸው ተመላክቷል፡፡

ተጨማሪ ያነቡ

20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን “ዲሞክራሲያዊ መግባባት፤ ለህብረ ብሄራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል በአሶሳ ከተማ በክልሉ መስተዳድር አዳራሽ በፓናል ውይይት እየተከበረ ነው፡፡

በውይይቱ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ የስራ ኃላፊዎችና የመንግስት ሰራተኞች በመታደም ላይ ሲሆኑ፤ ቀኑን በማስመልከትም የፌዴራሊዝምን አስተምህሮ በሚመለከት ረዳት ፕሮፌሰር አዳሙ ጅባት (የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የፌደራሊዝም መምህር)  የመወያያ ሰነድ በማቅረብ ላይ ናቸው፡፡   ከሰነዱ መቅረብ በኋላ ተሳታፊዎች ጥልቅ ውይይት በማድረግ የጋራ ግንዛቤ እንደሚያዝ ይጠበቃል፡፡

ተጨማሪ ያነቡ

22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን በዓል የታለመለትን ግብ እንዲመታ  አመራሮች የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ ጥሪ ቀረበ፡፡  

  22ኛው አለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን የታለመለትን ግብ እንዲመታ በየደረጃው የሚገኙ የክልሉአመራሮች፤ በተለይም በመስሪያ ቤቶች ኃላፊነት ተሰጥቷቸው የሚሰሩ የስነ-ምግባር መከታተያ ክፍል ባለሙያዎችን በማገዝ የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ የኮሚሽኑ የሙስና ወንጀሎችና ብልሹ አሰራር መከላከል ዳይሬክተር አቶ ጊሳ ዚፍሃ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ዳይሬክተሩ ይህን ያሉት ዛሬ በአሶሳ ከተማ የክልሉ መስተዳድር ቅጥር ግቢ  በክልል መስሪያ ቤቶች እና በአሶሳ ከተማ አስተዳደር […]

ተጨማሪ ያነቡ

22ኛውን አለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን በዓል መነሻ በማድረግ በተዘጋጀ ሰነድ ላይ ውይይት ተደረገ፡፡

      በሰነዱ በመንግስት መስሪያ ቤቶች እና የልማት ድርጅቶች የሚስተዋሉ፤ የተለያዩ የሙስና ዓይነቶች መዳሰሳቸውን ያወሱት የኮሚሽኑ የሙስና ወንጀሎችና ብልሹ አሰራር መከላከል ዳይሬክተር አቶ ጊሳ ዚፍሃ በተዋረድ የሚገኙ የመንግስት ተቋማት በሰነዱ ላይ በተነሱ ጉዳዮች ላይ  የሰላ ውይይት ማድረግ፣ የሙስና ወንጀል ተጋላጭነት ባለባቸዉ የዉስጥ አሰራሮች  ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ መያዝ፣ ችግሩን ለመፍታትም ጠንካራና ዘመኑን የዋጀ የፀረ-ሙስና ትግል […]

ተጨማሪ ያነቡ

22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን በክልል አቀፍ ደረጃ በተለያዩ ዝግጅቶች እንደሚከበር ኮሚሽኑ አስታወቀ፡፡

    22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን ታሪካዊውን የፀረ-ሙስና ትግል፤ ዓለም አቀፍ ትብብርና የቃል ኪዳን ቀን ከማስታወስ ባሻገር፤ በዕለቱ ሰፋፊ የፀረ-ሙስና ንቅናቄዎችን ማካሄድ፣ ለፀረ-ሙስና ትግሉ የታደሰ ቁመና መፍጠር፣ ሁሉን አቀፍ ትብብር፣ ትስስርና ቅንጅት ማረጋገጥን አላማ ማድረጉን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ከማል ሃሰን አስታውቀዋል፡፡   ዕለቱ በክልል ደረጃ ከህዳር 15 – 22/2018 […]

ተጨማሪ ያነቡ

‎በማዕድን ሀብት ላይ የሚስተዋለውን ሕገ-ወጥ አሠራር ለመከላከል የጀመራቸውን የቁጥጥር ሥራዎች የበለጠ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ማዕድን ቦርድ አስታወቀ፡፡  

‎ ‎የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የማዕድን ቦርድ ትላንት ባካሄደው ስብሰባ  ‎በማዕድን ሀብት ላይ የሚስተዋለውን ሕገ-ወጥ አሠራር ለመከላከል የጀመራቸውን የቁጥጥር ሥራዎች የበለጠ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል፡፡   ‎በክልሉ ያለውን የማዕድን ሀብት የአካባቢ ተጽእኖን በቀነሰ እና ዘላቂ ተጠቃሚነትን ባረጋገጠ መልኩ መጠቀም እንደሚገባም ቦርዱ አፅንኦት ሰጥቷል፡፡   ‎በሌላ በኩል በተለያዩ የማዕድን ዘርፎች ወደ ሥራ ለመግባት ፈቃድ ተሰጥቷቸው ወደ ልማት ያልገቡ […]

ተጨማሪ ያነቡ

የክልሉ ፖሊስ የሕብረተሰቡን ሰላም እያስጠበቀ ሕግን በማስከበር ሚናውን እየተወጣ ነው- ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን

    የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፖሊስ የሕብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት እያስጠበቀ የሕግ የበላይነትን በማስከበር ሚናውን እየተወጣ መሆኑን የክልሉ  ርዕሰ መስተዳድር  አሻድሊ ሀሰን ተናገሩ።   ርዕሰ መስተዳድሩ “ከጂኦስትራቴጂያዊ ኩስመና ወደ ታደሰ ቁመና” በሚል መሪ ሐሳብ ለክልሉ ፖሊስ እና ፀጥታ አካላት የሚሰጠውን ስልጠና አስጀምረዋል።   በዚህ ወቅት  ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን እንደተናገሩት፤ የፀጥታ አካላት ዋነኛው ተልዕኮ የሕብረተሰቡን […]

ተጨማሪ ያነቡ