22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን በዓል የታለመለትን ግብ እንዲመታ  አመራሮች የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ ጥሪ ቀረበ፡፡  

  22ኛው አለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን የታለመለትን ግብ እንዲመታ በየደረጃው የሚገኙ የክልሉአመራሮች፤ በተለይም በመስሪያ ቤቶች ኃላፊነት ተሰጥቷቸው የሚሰሩ የስነ-ምግባር መከታተያ ክፍል ባለሙያዎችን በማገዝ የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ የኮሚሽኑ የሙስና ወንጀሎችና ብልሹ አሰራር መከላከል ዳይሬክተር አቶ ጊሳ ዚፍሃ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ዳይሬክተሩ ይህን ያሉት ዛሬ በአሶሳ ከተማ የክልሉ መስተዳድር ቅጥር ግቢ  በክልል መስሪያ ቤቶች እና በአሶሳ ከተማ አስተዳደር […]

ተጨማሪ ያነቡ

22ኛውን አለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን በዓል መነሻ በማድረግ በተዘጋጀ ሰነድ ላይ ውይይት ተደረገ፡፡

      በሰነዱ በመንግስት መስሪያ ቤቶች እና የልማት ድርጅቶች የሚስተዋሉ፤ የተለያዩ የሙስና ዓይነቶች መዳሰሳቸውን ያወሱት የኮሚሽኑ የሙስና ወንጀሎችና ብልሹ አሰራር መከላከል ዳይሬክተር አቶ ጊሳ ዚፍሃ በተዋረድ የሚገኙ የመንግስት ተቋማት በሰነዱ ላይ በተነሱ ጉዳዮች ላይ  የሰላ ውይይት ማድረግ፣ የሙስና ወንጀል ተጋላጭነት ባለባቸዉ የዉስጥ አሰራሮች  ዙሪያ የጋራ ግንዛቤ መያዝ፣ ችግሩን ለመፍታትም ጠንካራና ዘመኑን የዋጀ የፀረ-ሙስና ትግል […]

ተጨማሪ ያነቡ

22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን በክልል አቀፍ ደረጃ በተለያዩ ዝግጅቶች እንደሚከበር ኮሚሽኑ አስታወቀ፡፡

    22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን ታሪካዊውን የፀረ-ሙስና ትግል፤ ዓለም አቀፍ ትብብርና የቃል ኪዳን ቀን ከማስታወስ ባሻገር፤ በዕለቱ ሰፋፊ የፀረ-ሙስና ንቅናቄዎችን ማካሄድ፣ ለፀረ-ሙስና ትግሉ የታደሰ ቁመና መፍጠር፣ ሁሉን አቀፍ ትብብር፣ ትስስርና ቅንጅት ማረጋገጥን አላማ ማድረጉን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ከማል ሃሰን አስታውቀዋል፡፡   ዕለቱ በክልል ደረጃ ከህዳር 15 – 22/2018 […]

ተጨማሪ ያነቡ

‎በማዕድን ሀብት ላይ የሚስተዋለውን ሕገ-ወጥ አሠራር ለመከላከል የጀመራቸውን የቁጥጥር ሥራዎች የበለጠ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ማዕድን ቦርድ አስታወቀ፡፡  

‎ ‎የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የማዕድን ቦርድ ትላንት ባካሄደው ስብሰባ  ‎በማዕድን ሀብት ላይ የሚስተዋለውን ሕገ-ወጥ አሠራር ለመከላከል የጀመራቸውን የቁጥጥር ሥራዎች የበለጠ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል፡፡   ‎በክልሉ ያለውን የማዕድን ሀብት የአካባቢ ተጽእኖን በቀነሰ እና ዘላቂ ተጠቃሚነትን ባረጋገጠ መልኩ መጠቀም እንደሚገባም ቦርዱ አፅንኦት ሰጥቷል፡፡   ‎በሌላ በኩል በተለያዩ የማዕድን ዘርፎች ወደ ሥራ ለመግባት ፈቃድ ተሰጥቷቸው ወደ ልማት ያልገቡ […]

ተጨማሪ ያነቡ

የክልሉ ፖሊስ የሕብረተሰቡን ሰላም እያስጠበቀ ሕግን በማስከበር ሚናውን እየተወጣ ነው- ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን

    የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፖሊስ የሕብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት እያስጠበቀ የሕግ የበላይነትን በማስከበር ሚናውን እየተወጣ መሆኑን የክልሉ  ርዕሰ መስተዳድር  አሻድሊ ሀሰን ተናገሩ።   ርዕሰ መስተዳድሩ “ከጂኦስትራቴጂያዊ ኩስመና ወደ ታደሰ ቁመና” በሚል መሪ ሐሳብ ለክልሉ ፖሊስ እና ፀጥታ አካላት የሚሰጠውን ስልጠና አስጀምረዋል።   በዚህ ወቅት  ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን እንደተናገሩት፤ የፀጥታ አካላት ዋነኛው ተልዕኮ የሕብረተሰቡን […]

ተጨማሪ ያነቡ

በክልሉ አዲሱ የመንግስት ሠራተኞች የመስከረም እና የጥቅምት ወራት የደመወዝ ጭማሪ ልዩነት ውዝፍ ክፍያ ከዛሬ ጀምሮ ለተቋማት እንደሚተላለፍ የክልሉ ምክትል ርዕሰ-መስተዳድር እና የሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌታሁን አብዲሳ ገለጹ  

  በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለመንግስት ሠራተኞች የተፈቀደው የመስከረም እና የጥቅምት ወራት የደመወዝ ልዩነት ውዝፍ ክፍያ ከዛሬ ጀምሮ ለተቋማት እንደሚተላለፍ የክልሉ ምክትል ርዕሰ-መስተዳድር እና የሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌታሁን አብዲሳ ገለጹ፡፡   የክልሉ ምክትል ርዕሰ-መስተዳድር እና የሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌታሁን አብዲሳ ጉዳዩን አስመልክተው ለሚዲያ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡   አቶ ጌታሁን አብዲሳ፣ መንግስት ከመስከረም 01/2018 […]

ተጨማሪ ያነቡ

በመፍጠርና በመፍጠን በመስራት ህዝቡን ተጠቃሚ ማድረግ ይጠበቅብናል፡- ርዕሰ መስተዳደር አሻድሊ ሀሰን

  የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን በየደረጃው ከሚገኙ የክልሉ መንግሥት አመራሮች ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ እየተወያዩ ነው፡፡   የክልሉን የመልማት አቅም፣ እስካሁን በተሰሩ ሥራዎች የተገኙ ስኬቶችንና ተስፋዎች እንዲሁም በቀጣይ ልዩ ትኩረት በመስጠት ሊሰሩ የሚገባቸውን ቁልፍ ተግባራት የተመለከተ የውይይት ሰነድ ርዕሰ መስተዳድሩ አቅርበዋል፡፡   በዚህም የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በተለያዩ የልማት ዘርፎች ማህበረሰቡን ተጠቃሚ […]

ተጨማሪ ያነቡ